ታላቁ የኢትዮጵያ የጥበብ ዝግባ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) (እ. ኤ. አ. 1935 – 2014) አረፈ

የጀርመን ሬዲዮ ጣቢያ የአማርኛ ክፍል ዘገባን ያዳምጡ

gemoraw1

ታላቁ የኢትዮጵያ የጥበብ ዝግባ ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) ስዊድን ውስጥ በሚኖርበት ሀገር፣ ባደረበት ሕመም ከዚህ ዓለም ተለየ። የሕዝብ ልሳን የሆነውን የጋሼ ኃይሉን ድንገተኛ ማለፍ ስንሰማ፣ የደብተራው ዝግጅት ቦርድ አባላት የተሰማን ድንጋጤና ሃዘን ከፍተኛ ነው። ዝርዝር ጉዳዮችን ወደፊት የምናቀርብ ሲሆን፣ ለመንደርደሪያነት የሚከተለውን አቅርበናል።

ይህ ታላቅ የጥበብ ሰው ኃይሉ ገብረዮሐንስ (ገሞራው) እ. ኤ. አ. በ1935 ዓ. ም. አዲስ አበባ ውስጥ ተወለደ። የተወለደበት ባህላዊው ቤት መሠረቱ የተጣለው የዛሬው የአፍሪካ አንድነት ድርጅት ከተሰራበት ቦታ ላይ ነበር። ከህፃንነቱ አንስቶም ቄስ እንዲሆን ይፈልጉ የነበሩት አባቱ መሪ ጌታ ገብረዮሐንስ የቤተክርስቲያን ትምህርት እየሰጡት ነው ያደገው።  ሙሉውን ያንብቡ …