የገሞራውን አስክሬን ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠት ስለሚደረገው ደባ ተጨማሪ ዘገባ

የታላቁን ኢትዮጵያዊ የጥበብ ሰው የኃይሉ ገብረዮሐንስን (የገሞራውን) አስክሬን ለወያኔ አሳልፎ ለመስጠት የሚደረገው ደባ አሁንም ተጠናክሮ ቀጥሏል።  ውስጥ አወቅ gemoraw1ምንጫችን እንዳረጋገጠልን፣ የደባው አንቀሳቃሽ ቡድን ስዊድን፣ ስቶክልሆም ውስጥ ሰሞኑን ስብሰባ አድርጎ ለወያኔ ኤምባሲ አቀረበ የተባለው ጥያቄ ከታላቁ የጥበብ ሰው እና የሕዝብ ልጅ ከገሞራው ፎቶ ጋር በአገዛዙ  አምባሳደር በወይንሸት ታደሰ በኩል አዲስ አበባ ላለው የወያኔ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ተልኳል።  የወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ቴዎድሮስ አድሃኖም በሀገር ቤት ሰላልነበረም፣ ጉዳዩ በወያኔው ጠቅላይ ሚ/ር ቢሮ ውስጥ፣ በሚ/ር ማዕረግ የዲያስፖራ ጉዳይ አማካሪ ለሆነው ለእንድሪያስ እሸቴ ቀርቦ፣ እሱም በበኩሉ  የወያኔውን ኤምባሲ ጥያቄ ለበረከት ስምዖን መርቶት ነበር።  እጁ በደም የታጠበው ስምዖን በረከትም ከደም አፍሳሽ ጓደኞቼ ጋር ልመካከርበት ብሎ፣ ከነ ስብሃት ነጋ እና ሌሎቹም የወያኔ ቁንጮዎች ጋር ከተመካከረ በኋላ፣ የወያኔ የውጭ ምንዛሬ ላም እና አፍኖ መግዣ የሆነው አየር መንገድ በቅናሽ ዋጋ አስክሬኑን ወደ ኢትዮጵያ እንዲያጓጉዝ ፈቅደዋል ተብሏል።  ሙሉውን ያንብቡ …