በትምህርት ሥርዓቱና በመምህራን ላይ የተደቀነ አደጋ

በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማኅበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ:  በታሪክ አጋጣሚ በሥልጣን ላይ የተቆናጠጡ ገዢ ሃይሎች ሁሉ ሕዝብ የሚያነሳቸውን የመብት ጥያቄዎች በአግባቡ ሲመልሱ አልታዩም። ከሕዝብ ፍላጎትና ጥያቄ ይልቅ የራሳቸውን የፖለቲካ ፍላጎትና ጥቅም በማስቀደም ሕዝቡን ለርሃብ፣ ለድንቁርና፣ ለስደትና ውርደት፣ አገሪቷን ለውድቀት ዳርገዋል።  በተለይ ወያኔ/ኢህአዴግ በመማር ማስተማር ሙያ ላይ የተሰማራውን ሃይል የተለያዩ ስያሜዎችን በመስጠትና በወያኔያዊ ግምገማ በማስመረር ልምድ ያካበቱ መምህራንን ከሥራ ማባረሩና ሙያውን ለቀው እንዲሄዱ ተጽዕኖ ማድረጉ ለትምህርት ውድቀት አመላካች አርምጃ ነው።  ሙሉውን  መግለጫ ያንብቡ