Poems


 

.

የሞት ጉራማይሌ

(ከአብርሃም በየነ)

 

በማዳበሪያ መርዝ፣ ተብክሎ አፈሩ፣

በሞት ጥላ ግርዶሽ፣ ተከልሎ ምድሩ፣

እንደ ቅጠል ሲረግፍ፣ በላዩ ፍጥረቱ፣

የሞት ሳል ይስላል፣ እንደ ሰው መሬቱ።

ሙሉውን ግጥም ያንብቡ

ተረት ተረት

(ከሄኖክ . የሺጥላ) 

 

ተረት ልንገርሽ ህይወቴ፣

እንቺ አድምጪኝ በሞቴ፣

ተረት ቢሉሽ ተረት ተረት፣

የዘመነኛችንን ምጥቀት፣

አዲሱን ኢትዮጵያዊነት

እየጠፉ አለሁ ማለት፣

እየጠፉ ያልፋል ማለት፣

ተረት ትረት።

ሙሉውን ግጥም ያንብቡ…

እስቲ ተጠየቂ

እስቲ ልጠይቅሽ፣

ምትክ ለልጆችሽ፤

ላንቺ በደከሙ ላንቺ በሞቱልሽ፤

እነማንን ተካሽ ?!

እነማንን ወለድሽ ?!

ሙሉውን ግጥም ያንብቡ…

እሽሩሩ – ሩሩ – ኦሶ ሃዬ ሃዬ

(ከገንባው) 

መቼ ንብረታቸውን፣ ባንካቸውን ደፍሮ፣

ጣቱን ቀስሮ እንጂ፣ መቼ እጁን ሰንዝሮ፣

ገዳዩስ ድምፁ ነው፣ ጠንቀኛው ጉሮሮ።

ልጄ አፍህን ዝጋ! አታልቅስ ላይረባ፣

በየአምስት አመቱስ፣ እኔስ ለምን ላንባ፣

ድምጽህ ጠላትህ ነው፣ ጉልበትህን ገንባ።

ሙሉውን ግጥም ያንብቡ …

 

ለሳሙኤል ዓለማየሁ

እህታቸው ሀና ዓለማየሁ ያቀረቡትን የሀዘን እንጉርጉሮ ያንብቡ

ሀማ ቱማ

ቆሞ መሄድ ከብዶ፣ ሰብዕናን ጠብቆ፣

መንበርከኩ ሰፍኖ፣ ከጭቃው ውስጥ ገብቶ፣

የሰው  ሰውነቱ ትርጉሙ ሲፈለግ፣

ባሻገር፣ ባሻገር

ከአስመሳይነቱ፣

ከአፋዊው ፋኖ፣

ሙሉውን ግጥም ያንብቡ …

ቆንጆ የሁሉም ናት


አሥራደው (ከፈረንሳይ)

 

አንደኛው  አግኝቶ፣  ውዴ  ፍቅሬ  ሲላት፣

ሌላው  በማጣቱጧት  ማታ  ሲመኛት፣

የውበት  ዕድምተኞች፣  እያዩ  ሲያደንቋት፣

ያላየው  እያየ፣  ውበቷን  ሲጎመዥ፣

ምኞቱን  ለማስመር፣  ዐይኑ  ሲንቀዠቀዥ፣

የሰማው ላልሰማ፣ ዝናዋን ሲረጨው፣

በውበት ረሃብ፣  ምራቁን ሲያስውጠው፣


More >