“ሀገርንና ሕዝብን ባለመክዳታችን ፤ አብሮን የሚኖረው ኅሊናችን ሲያመስግነን ይኖራል!”

ከፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ ሀተታ - የኢሕአፓ ታጋዮች፤ እንደ አብረሐም ቤት የሌላቸው፤ እንደ ሙሴ መቃብራቸው ያልታወቀላቸው፤ የቤተስብ ባይታዎሮች፤ የዓለም ተንከራታቾች መሆናቸውን ያውቃሉ። በዚህ አይቆጩም። ነገር ግን፤ ፓርቲያቸው የወቀሳ ዶፍ እንጅ፤ የምስጋና ካፊያ ያልተቸረው በመሆኑ ....

Continue reading

በጎጃም ዳንግላ ዜጎችን የገደለና ያስገደለው ተገደለ፣ የወያኔ ሃይሎችም በባህርዳርና በቦረናም ዜጎችን ገደሉ፣ ኢትዮጵያዊያን ወደሃገር ቤት የሚልኩት የውጭ ምንዛሬ ቀንሷል …

ፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ ሬዲዮ (ጥር 09 ቀን 2009 ዓ.ም.): በጎጃም ክፍለ ሀገር በዳንግላ ዜጎችን የገደለና ያስገደለ ፖሊስና ነጋዴ ተገደለ - የወያኔ የጸጥታ ኃይሎች በባህር ዳር ዜጎችን መግደል ቀጥለዋል - በቦረና አካባቢ የወያኔ ልዩ ....

Continue reading

ወያኔ የሰላማዊ ትግል አስተባባሪዎችን በሽብርተኛነት ከሰሰ፣ የህዝብን ትግል አቅጣጫ ለማስቀየርም ባለሥልጣኖቹን አሳሰረ

ፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ (ጥር 06 ቀን 2009 ዓ.ም.) - ንግስት ይርጋና ሌሎች አምስት ተባባሪዎች በሽብረተኛነት ተከሰሱ  - የሕዝብን ድጋፍ ለማግኘት ወያኔ ባለስልጣኖችን መወንጀልና ማሰሩን ቀጥሏል - በኢትዮጵያ የሥራ አጡ ቁጥር ከፍተኛ ነው። በጎንደር ....

Continue reading

የኢትዮጵያ ፈተናዎችና መፍትሔ መንገዶች አስተያየት

በቀለ ገሠሠ (ዶ/ር): እዚህ ላይ አንድ እዉነታን ማስጨበጥ እፈልጋለሁ። ኢትዮጵያ ያፈራቻቸዉ እጅግ በጣም ብሩህ የነበሩ ወጣቶች፤ መምህራን፤ መሃንዲሶች፤ ነርሶች፤ ዶክተሮች፤ ወዘተ ለዲሞክራሲና ለእኩልነት ሲሉ የከፈሉትን የሕይወት መስዋዕትነት ታሪክ ሲያስታዉስ ይኖራል።  ዛሬ ወደኋላ እየተመለከቱ እነዚያ ተማሪዎች ....

Continue reading

የኢትዮጵያ ወጣቶች ቀጣይ ትግል ቀጣይ ቃል ኪዳን

(ዴሞክራሲያ: የኢሕአፓ ልሳን፣  ቅጽ 42፣ ቁ. 3፣ ታኅሣሥ 2009):  በወጣትነት እድሜያቸው ኢሕፓን የመሠረቱትም ሆነ በኋላም የድርጅቱ አባልና ደጋፊ በመሆን በትግሉ ውስጥ የተሳተፉት ወጣት ምሁራንና ተማሪዎች ከሁሉም የኅብረተሰብ ክፍል በኢትዮጵያዊነት የተሰባሰቡ፤ በአንድ ዓላማና ፍላጎት ( በአገር ....

Continue reading

በባህርዳር ከተማ ውጥረቱ ተባብሷል፣ ኢትዮጵያዊያን በዚምባብዌ ፍርድ ቤት ቀረቡ . . .

ፍኖተ ዴሞክራሲ የኢትዮጵያ አንድነት ድምጽ ሬዲዮ (ታኅሣሥ 28 ቀን 2009 ዓ.ም.) - በባህር ዳር ከተማ ውጥረቱ ተባብሷል  - በዚምባብዌ እርሻ ውስጥ ተደብቀው የተገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ፍርድ ቤት ቀረቡ - በአይቮሪ ኮስት ታላላቅ ከተሞች ወታደሮች የአመጽ ....

Continue reading